Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል 1 ነጥብ 55 ቢሊየን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ ተደርገዋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል በዘንድሮው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቅቋል አለ የክልሉ ግብርና ቢሮ።

በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ÷ ለ2017 ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 1 ነጥብ 6 ቢሊየን በላይ ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል፡፡

አሁን ላይም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው 1 ነጥብ 55 ቢሊየን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ መደረጋቸውን ነው ለፋና ዲጂታል የተናገሩት፡፡

ከተዘጋጁ ችግኞች ውስጥ ፍራፍሬ፣ ሀገር በቀል የደን ችግኞች፣ የእንስሳት መኖ እና ሌሎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡

ለመርሐ ግብሩ በቂ የመትከያ ቦታ መዘጋጀቱን ጠቁመው÷ በአሁኑ ወቅት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ጉድጓድ መቆፈሩን አንስተዋል፡፡

በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የችግኝ ተከላ መጀመሩን የገለጹት ዳይሬክተሩ÷ በሐምሌ ወር መጀመሪያ ቀናት ክልል አቀፍ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር እንደሚካሄድ አመልክተዋል፡፡

ከመርሐ ግብሩ ጋር በተያያዘ ለመትከያ ቦታዎች የካርታ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን የማዘጋጀት ሥራ መጠናቀቁንም አስረድተዋል፡፡

የክልሉ ሕዝብ እንደወትሮው በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በንቃት እንዲሳተፍም አቶ እስመለዓለም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.