ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ በሐረር ከተማ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አራተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2017 ዓ.ም በሐረር ከተማ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የሰላም ጉባኤውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ ጉባኤው በሃይማኖት ተቋማት መካከል ያለውን ትስስር ያጠናክራል ብለዋል።
በመድረኩ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች እንደሚገኙ ገልጸዋል።
የሰላም ጉባኤው በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት አስተዋጽኦ ይኖረዋል ነው ያሉት።
በተጨማሪም ችግሮችን በውይይት የመፍታት ልምዶችን ለማዳበር ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፤ በጉባኤው የፓናል ውይይቶችና ህዝባዊ ኮንፈረንስ እንደሚኖር ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም በድሬድዋ፣ በጅማ፣ በባህርዳር በተካሄዱ የሰላም ጉባኤዎች ህብረተሰቡ የሰላም ባለቤት እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
በተለይም የሃይማኖት ተቋማት እርስ በርስ በመቀራረብ የመደጋገፍ ባህል አዳብረዋል ብለዋል።
በቅድስት ብርሃኑ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!