Fana: At a Speed of Life!

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሥርዓተ ቀብር በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ተፈጽሟል።

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ ከተካሄደ በኋላ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሃላፊዎች፣ የላጲሶ (ፕ/ር) ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል።

የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምና ሲከታተሉ ቆይተው ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡

ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የታሪክ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የተለያዩ የታሪክ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አበርክተዋል፡፡

የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴት፣ ባሕልና ቋንቋ በማውሳት የሕዝቦች ታሪክ ጎልቶ እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተው አልፈዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.