በሀረሪ ክልል የምርጫ ጣቢያዎች ዝግጅት እያደረጉ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀረሪ ክልል በነገው ዕለት ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጮችን ለማስተናገድ የምርጫ ጣቢያዎች ዝግጅት እያደረጉ ነው።
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሀረር ከተማ ባደረገው ቅኝት የምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
በምርጫ ጣቢያዎቹ ጊዜያዊ መጠለያዎችን ጨምሮ አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁስ እየተሟሉ ይገኛሉ፡፡
በተሾመ ኃይሉ
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትመርጣለች #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል #Election #fanadigital #Ethiopia #Ethiopiavotes #Democracy #fanatelevision