Fana: At a Speed of Life!

የሀገር ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት ማምረት ስንችል ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዐት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነትና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት፣ በራስ ክህሎት እና በራስ ቴክኖሎጂ ማምረት ስንችል ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዐት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነት እና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት፣ በራስ ክህሎት እና በራስ ቴክኖሎጂ ማምረት ስንችል ነው ብለዋል፡፡

መንግሥት በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የታለመውን ዘላቂ ዕድገት እና ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ፖሊሲዎችን አሻሽሏል፤ አሠራሮችን ዘርግቷል፤ ማበረታቻዎችን አድርጓል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የዚህ ሪፎርም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ፍሬው በግልጽ እየታየ እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.