Fana: At a Speed of Life!

የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን አስመልክቶ ለውጭ ሀገር ኢንቨስተሮች ገለፃ እየተደረገላቸው ነው

አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን አስመልክቶ ለውጭ ሀገር ኢንቨስተሮች ገላፃና ማብራሪያ የተደረገላቸው ነው።

ለውጭ ሀገር ኢንቨስተሮች በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረጉት የወንጪ ፣ ጎርጎራ እና ጨበራ ጩርጩራ ፕሮጀክቶች ነው ገለፃ እየተደረገላቸው የሚገኘው።

በዚህም ስለፕሮጀክቶቹ አጠቃላይ ዝርዝር ፍላጎትና ተግባራዊነት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር አብረሃም በላይ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣም ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ እና የጎርጎራ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ዶክተር ፍሰሃ ተገኝ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።

በገለጻውም ፕሮጀክቶቹ በውስጠቸው ስለሚይዟቸው ፣ ስላላቸው የቱሪስት መስህብ እና ተፈጥሮአዊ አቅም እንዲሁም ስለሚፈጥሩት የስራ እድል ተነስቷል።

ባለሃበቶቹም ለፕሮጀክቶቹ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

በሀብታሙ ተ/ስላሴ

#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.