Fana: At a Speed of Life!

ህብረተሰቡ በፕሮፓጋንዳ ሳይደናገጥ የአካባቢውን ሠላምና ደህንነት ሊጠብቅ ይገባል – የደሴ ከተማ አስተዳደር የሠላምና ደህንነት መምሪያ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ህብረተሰቡ በሐሰት ፕሮፓጋንዳ ሳይደናገጥ የአካባቢውን ሠላምና ደህንነት ነቅቶ ሊጠብቅ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር የሠላምና ደህንነት መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሐሰን መሃመድ እንደገለጹት የህወሓት ጁንታ በደሴ ከተማ ገባ እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ የተለመደ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡

መላው የደሴ ከተማና የአካባቢው ማህበረሰብም የህወሓት ጁንታ በሚያስተላልፈው የአሉባልታ ወሬ ሳይደናገጥ የአካባቢውን ሠላምና ደህንነት ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው ተደራጅቶ መጠበቅ ይገባዋል ብለዋል፡፡

የጁንታውን ሃገር የማፍረስ ሴራ በመመከት በቀጠናው አስተማማኝ ሠላምና ደህንነት እንዲሰፍን ከአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ጋርም በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከደሴ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ የወጣት አደረጃጀቶች፣ ማህበራት፣ እድሮች፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር የከተማዋን የመውጫና የመግቢያ በሮችን በተጨማሪም የመኝታ አገልግሎት የሚሰጡ ቤቶች ላይም የተናጠከረ ልዩ ፍተሻና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በይከበር አለሙ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.