Fana: At a Speed of Life!

ለድምጻዊ አህመድ ሁሴን (ማንጁስ) በትውልድ ከተማው ኮምቦልቻ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)የፋና ላምሮት የባለተሰጥኦ ድምፃውያን ውድድር አሸናፊው አህመድ ሁሴን (ማንጁስ) በትውልድ ከተማው ኮምቦልቻ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባዘጋጀው የድምፃውያን ውድድር የ1ሚሊየን ብር እና የዋንጫ ተሸላሚ የነበረው አህመድ ሁሴን ÷ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የከተማ አስተዳደሩ እና የዞን አመራሮች በተገኙበት በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

የደቡብ ወሎ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኀላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ በአቀባበል ስነስርዓቱ እንዳሉት÷ ድምፃዊ አህመድ ከአሸናፊነት በላይ ወሎ የቅኝት መሠረት መሆኗን አስመስክረሀል ብለዋል፡፡

ለድምጻዊው የተለያዩ ድርጅቶች እና ግለሰቦች 4መቶ ሺህ ብር ማበርከታቸውም ተናግሯል፡፡

በእሸቱ ወ/ሚካኤል

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.