Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወም ሰልፍ እያካሄዱ ነው

አዲስ አበባ፣ ህዳር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት በኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ያለውን ጫና የሚቃወም ሰልፍ እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡

ሰልፉ በኢትዮጵያ ላይ የሚካሄደው ጣልቃ ገብነት ”ይብቃ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ ያለው፡፡

የዩኒቨርሲቲው አባላት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እና የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ የሚከናወነው መርሃ ግብር እንደተጠናቀቀ÷ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት በአሜሪካ ኤምባሲ በር ላይ በመገኘት ተቃውሟቸውን እንደሚያሰሙ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.