በማክሮ ኢኮኖሚው በተወሰደው እርምጃ ለውጥ ተመዝግቧል- መንግስት
ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገቡ ከሚገኙት የወጪ ንግድ የገቢ ማስገኛ ምርቶች ውስጥ ቡና ዋነኛው መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ ቡና ከጠቅላላ የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ ላይ የ33 በመቶ ድርሻ እንደሚይዝ ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ወራት ወደ ውጪ የተላከው የቡና ምርት ከባለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነፃጸርም የ61 ነጥብ 5 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ነው የገለጹት፡፡
ከቡናው ዘርፍ በወጪ ንግድ የተገኘው አጠቃላይ ገቢም 329 ሚሊን የአሜሪካ ዶላር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ከቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ጭማሪ ማሳየቱን ነው ያብራሩት፡፡
በቀጣይም የአገር ውስጥ ምርትን መጨመር፣ የሸቀጦችን አቅርቦት የማሻሻል እና በግብይት ሰንሰለቱ ውስጥ የሚስተዋሉ አሻጥሮችን መቆጣጠር ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡