በምዕራብ ወለጋ ዞን 37 የሸኔ አባላት በሰላም እጃቸውን ሰጡ
አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጋንጂ ወረዳ 37 የሸኔ አባላት በሰላም ለመንግስት እጃቸውን መስጠታቸውን የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
አባላቱ የክልሉ መንግስት እና አባገዳዎች ያቀረቡትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ነው እጃቸውን የሰጡት፡፡
በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪው የሸኔ ቡድን ለመደምሰስ አስፈላጊው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!