Fana: At a Speed of Life!

የተጎዱ ተቋማትን ለመደገፍ እና ከስደት ተመላሾችን ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ እና አፋር ክልሎች የተጎዱ ኢንተርፕራይዞችን እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ለመደገፍ እንዲሁም ከስደት ተመላሾችን ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በሁለቱም ክልሎች የሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት፣ ጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በጦርነቱ ምክንያት የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የሚያሳይ እና ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በሚመለከት የችግሩን ግዝፈት የሚያመላክት መነሻ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት መካሄዱም ተገልጿል፡፡
በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር በከር ሻሌ እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰማሪታ ሰዋሰው ተገኝተዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ የጀመሯቸውን እንቅስቃሴዎች፣ መስተካከል ያለባቸውን አሰራሮች እና የጉዳቱን ሁኔታ በሚመለከት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዎቹ በበኩላቸው÷ ያጋጠሙ ችግሮችን መንግስት ብቻውን መቋቋም ስለማይችል ኢንተርፕራይዞችን፣ ቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ለመደገፍ እና ከስደት ተመላሽ ዜጎችን ለማቋቋም ድጋፍ ማድረግ የጀመሩ አካላትን አመስግነዋል፡፡

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አጋር የሆኑ ድርጅቶች ለዚህ ተግባር እንዲተባበሩ ሚኒስትር ዲኤታዎች መጠየቃቸውን ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.