Fana: At a Speed of Life!

በህልውና ዘመቻው ለተሳተፉ የጎንደር ከተማ ጤና ባለሙያዎች እውቅና ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ በህልውና ዘመቻው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤና ባለሙያዎች ፣ የአምቡላንስ ሹፌሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ዕውቅና ተሰጥቷል፡፡

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባዘጋጀው መርሃ-ግብር የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ዘውዱ ማለደ ÷ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ሀገር በጠላት እንዳትወረር በሙያችሁ ላደረጋችሁት ሀገራዊ አበርክቶ ምስጋና እና ዕውቅና ይገባችኋል ሲሉ ባለሙያዎችን አመስግነዋል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በለጠ ፈንቴ ÷ በህልውና ዘመቻው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 43 የጤና ባለሙያዎች፣ አምሥት የአምቡላንስ ሹፌሮች እና ሥምንት ጤና ጣቢያዎች ዕውቅና መሠጠቱን ተናግረዋል፡

ኃላፊው አክለውም ሁለት የዕርዳታ ድርጅቶች ፣ የጎንደር ደም ባንክ ፣ ጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፣ ለመድሃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ እና ለግል ጤና ተቋማት ዕውቅና እንዲሁም የዋንጫና የምስጋና የምስክር ወረቀት መሠጠቱንም ጠቁመዋል፡፡

በአበራ መኮንን

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.