የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴው ስራ መጀመሩን አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ ስራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬደዋን ሁሴን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በኩል እንዳስታወቁት፥ የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴው የመጀመሪያ ስብሰባውን አካሂዷል።
ኮሚቴው በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለሚካሄደው የሰላም ውይይት የራሱን የአሰራርና ሥነምግባር አካሄድ ተወያይቶ መወሰኑንም አምባሳደር ሬድዋን ጠቁመዋል፡፡
አብይ ኮሚቴው በንዑሳን ኮሚቴዎች በመደራጃትም ኃላፊነት ተከፋፍሎ ስራውን መጀመሩንም አስታውቀዋል፡፡
በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ችግር የሰላም አማራጮች እንዲታዩ እና የፌደራል መንግስቱን ወክለው በሰላም ውይይቱ ላይ የሚሳተፉ አባላት መመደባቸው ይታወሳል።
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!