ተቋርጦ የነበረው የማኒላ ከተማ በረራ መቀጠሉን አየር መንገዱ አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፊሊፒንስ የንግድና ፋይናንስ ማዕከል ወደሆነችው ማኒላ ከተማ ተቋርጦ የነበረው በረራ መቀጠሉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል፡፡
በዚሁ መሰረት÷ ወደ ማኒላ ከተማ የሚደረገው በረራ በሳምንት ሦስት ቀን ሆኖ መቀጠሉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ያመላክታል፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!