የመጨረሻው የአፈር ማዳበሪያ በየብስ ትራንስፖርት ተጓጉዞ ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመጨረሻው የአፈር ማዳበሪያ በየብስ ትራንስፖርት ተጓጉዞ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ እንዳስታወቀው÷ የአፈር ማዳበሪያ 10ኛ ዙር 500 ሺህ ኩንታል ዩሪያ ማዳበሪያ በየብስ ትራንስፖርት ተጓጉዞ ተጠናቋል፡፡
ከጥር ወር ጀምሮ እስካሁን ድረስ 1 ሚሊየን 282 ሺህ 317 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ በድርጅቱ በኩል የተጓጓዘ ሲሆን÷ ይህም በዓመቱ ሊጓጓዝ ከታቀደው 99 ነጥብ 6 በመቶ መሳካቱን ያሳያል ተብሏል፡፡
በግብርና ኮርፖሬሽን የተገዛውን የአፈር ማዳበሪያ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት÷ ከሞሮኮ፣ ከዩናይትድ ዓረብ ኤምሬትስ እና ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ አጓጉዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!