Fana: At a Speed of Life!

የጤና ሚኒስቴር ያሰባሰበውን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስረከበ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማትና ሠራተኞቹ ያሰባሰበውን የትምህርት ቁሳቁስ ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስረከበ።

ድጋፉን ያስረከቡት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ÷ ይህኛው ድጋፍ የበፊቶቹ ጊዜያትድጋፎች አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዓላማውም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወላጆችን ካለባቸው ጫና ማሳረፍ ነው ብለዋል ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተሰጠው ዋነኛ ተልዕኮ በተጨማሪ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝም ሚኒስትሯ ገልጸዋል፡፡

ከ 1 ሚሊየን በላይ ዜጎች በጤና ሚኒስቴር የነፃ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ  መደረጉንም ነው የጠቆሙት፡፡

ባለፉት ዓመታት በሥፋት ሲተገበር በቆየው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ÷  የጤና ሚኒስቴርም በአዲስ አበባ እና በጋምቤላ ክልል የአቅመ ደካማ አረጋውያንን ቤት በማደስ እንደተሳተፈም ገልጸዋል።

ድጋፉ ለ900 ተማሪዎች የሚከፋፈል ሲሆን በወቅቱ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ  ተቀብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.