Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ማቆማቸው ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ማቆማቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው የሚገኙ 6 ታካሚዎች ናቸው።

ከእነዚህ ውስጥ አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ያቆሙና በደህና ሁኔታ ላይ የሚገኙ ናቸው ተብሏል።

ሁለቱ ታካሚዎች በማገገም ላይ በመሆናቸው የቅርብ ህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.