Fana: At a Speed of Life!

የፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ገለጸ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ።

የፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር እስክንድር ሳህሉ እስካሁን የቫይረሱ ምልክት ታይቶባቸው ወደ ሆስፒታሉ የመጡ ታማሚዎች አለመኖራቸውን ተናግረዋል።

ይሁን እንጅ የቫይረሱ ምልክት የታየባቸው ሰዎች ወደ ሆስፒታሉ ቢመጡ ወደ ማቆያ ክፍል እስከሚሄዱ ድረስ ተገልለው የሚቆዩበት ቦታ መዘጋጀቱንም ነው የተናገሩት።

አያይዘውም የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)፣ የመተንፈሻ አካል ችግር፣ ሳል፣ ትኩሳት እና የጉዞ ታሪክ ያላቸውን በጥርጣሬ እንዲያዩ እና ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሏቸው ለህክምና ባለሙያዎች ትዕዛዝ መሰጠቱንም ገልጸዋል።

የቫይረሱ ምልክቶች ያለባቸው ባጋጠሙ ጊዜ በሆስፒታሉ የመጀመሪያ እርዳታ ከተሰጠ በኋላ ለበለጠ ምርመራ ወደ ተዘጀጋጁላቸው ማዕከላት እንዲላኩ ይደረጋልም ነው ያሉት።

መረጃው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ነው

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.