Fana: At a Speed of Life!

ዩኒቨርስቲዎች የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን መቀበላቸውን ቀጥለዋል

 

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን እየተቀበሉ ነው፡፡

 

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘጠኝ ካማፓሶች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

 

በተመሳሳይ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ÷ የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው ፡፡

 

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲም÷ 37ሺህ ተፈታኝ ተማሪዎች የሚቀበል ሲሆን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ቅበላ እንደተደረገላቸው ታውቋል።

 

ደብረ ማርቆስ፣ አሶሳ እና ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲዎችም ዝግጅታቸውን በማጠናቀቅ ተፈተኛ ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚገኙ መግለጻቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.