ዩኒቨርስቲዎች የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን መቀበላቸውን ቀጥለዋል
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን እየተቀበሉ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘጠኝ ካማፓሶች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።
በተመሳሳይ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ÷ የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው ፡፡
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲም÷ 37ሺህ ተፈታኝ ተማሪዎች የሚቀበል ሲሆን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ቅበላ እንደተደረገላቸው ታውቋል።
ደብረ ማርቆስ፣ አሶሳ እና ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲዎችም ዝግጅታቸውን በማጠናቀቅ ተፈተኛ ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚገኙ መግለጻቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡