ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ከእንግሊዝ የዌሴክስ ልዕልት ሶፊ ራይስ-ጆንስን ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ ካሉት ከእንግሊዝ የዌሴክስ ልዕልት ሶፊ ራይስ-ጆንስን ጋር በተለያዩ ሰብዓዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸው ዓይነ ስውርነትን በማጥፋት ዙሪያ፣ በጦርነት ወቅት የሚደርሱ ጾታዊ ጥቃቶችን በመከላከልና በሠላምና ፀጥታ የሴቶች ሚና ላይ መክረዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ በውይይታቸው ወቅት÷ የልዕልቷ ጥረት የሚያስመሰግን መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለእነዚህ የሰብዓዊ ጉዳዮች ትኩረት እንደምትሰጥ መግለጻቸውን ከፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡