አሸባሪው ህወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ የፈፀመው ጥቃት መታሰቢያ ነገ በተለያዩ ክልሎች ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሽብርተኛው ህወሓት በመከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ የፈፀመው ጥቃት ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ ነገ በሲዳማና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በተለያዩ ዝግጅቶች ይካሄዳል፡፡
የሲዳማ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ኢያሱ ዳዊት እንደገለፁት÷ መታሰቢያው በክልሉ በሁሉም ወረዳዎች የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ክብር በሚያጎሉ ዝግጅቶች ይከናወናል፡፡
በሠራዊቱ ተጋድሎ እና በሕዝቡ የደጀንነት ሚና ላይ ያተኮረ ውይይት እንደሚካሄድ የክልሉ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሁሉም ወረዳዎች፣ ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ ነዋሪዎች፣ የመንግስት ሠራተኞች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አስበው እንደሚውሉ የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡