Fana: At a Speed of Life!

አመራሩ ሕዝብ እና መንግሥት የጣለበትን ኃላፊነት በቁርጠኝነት ሊወጣ ይገባል – አቶ ኦርዲን በድሪ

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በክልሉ በ2015 የመጀመሪያው ሩብ አመት የተሰሩ ስራዎችን ገምግሟል።

በግምገማው የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንደገለፁት በክልሉ በመጀመሪያው ሩብ አመት አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል።

በተለያዩ ዘርፎች ውስንነት የታየባቸው እና ሊሻሻሉ የሚገባቸው አፈፃፀሞች መኖራቸውን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም የአመራሩ ቁርጠኝነት ማነስ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም የህዝብን ተጠቃሚነት ለማጎልበት በሚከናወኑ ተግባራት አመራሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩም የተለያዩ ሀሳቦችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን ለመቅረፍ፣ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጎልበት እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን በሚቻልባቸው ጉዳዮች  መግባባት ላይ መደረሱን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.