Fana: At a Speed of Life!

በደብረ ብርሃን ከ100 ሺህ በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመጠጥ ውኃ ማስፋፊያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማስፋፊያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡

ማስፋፊያው በ75 ሚሊየን ብር ወጪ የሚገነባ መሆኑ ተገልጿል።

የከተማዋ የመጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መሰረት መንገሻ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ማስፋፊያው ከ100 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁሕ መጠጥ ውኃ ችግር የሚቀርፍ ነው።

የማስፋፊያ ሥራው በአንድ ዓመት እንዲጠናቀቅ መታቀዱን እና ወጪውም በጽሕፈት ቤቱ መሸፈኑን ተናግረዋል፡፡

በዓይናለም ስለሺ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.