Fana: At a Speed of Life!

ቻይና በታይዋን ዙሪያ ወታደራዊ ልምምድ ጀመረች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቻይና ጦር በዛሬው ዕለት በታይዋን አቅራቢያ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

በልምምዱም የውጊያ ዝግጁነት ቅኝቶች እና ወታደራዊ ስልጠናዎች መካሄዳቸውን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡

ልምምዱም “ታይዋን እና ውጫዊ ኃይሎች” ለሚያደርጉት ጠባጫሪ ድርጊት ከባድ ማስጠንቀቂያ መሆኑን የቤጂንግ ጦር ገልጿል፡፡

እንዲሁም በቻይና በኩል “የሉዓላዊነትና የግዛት አንድነትን ለማስጠበቅ ተገቢ እንቅስቃሴ” መሆኑ ተመልክቷል፡፡

የልምምዱ የመጀመሪያ ቀን ውሎ የተካሄደው÷ ከታይዋን ደሴት በስተሰሜን እና በደቡብ ታይዋን የባሕር ዳርቻ ዙሪያ እንዲሁም ከደሴቲቱ በስተምሥራቅ ባለው የአየር ክልል እና ባሕር ላይ ነው፡፡

የታይዋን መከላከያ ሚኒስቴርም በዛሬው ዕለት በደሴቲቱ ዙሪያ 42 የቻይና አውሮፕላኖች እና 8 መርከቦችን አግኝቻለሁ ማለቱን ጠቅሶ አር ቲ ዘግቧል፡፡

ልምምዱ የተጀመረው የታይዋን መሪ ጻይ ኢንግ ዌን ከአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ኬቨን ማካርቲ እና ሌሎች የምክር ቤቱ እንደራሴዎች ጋር ተገናኝተው ከተመለሱ አንድ ቀን በኋላ ነው።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.