የፋሲካ እና የዒድ አልፈጥር በዓላትን አንድነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ማክበር እንደሚገባ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፋሲካ እና የዒድ አልፈጥር በዓላትን አንድነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ማክበር አለብን ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ።
ከንቲባው መጪዎቹን በዓላት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም÷ የፋሲካ እና የዒድ አልፈጥር በዓላትን የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ እና የእርስ በእርስ አንድነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ማክበር ይገባል ብለዋል።
በዓላቱን የእርስ በእርስ ግንኙነትን በማጎልበት የሀገርን ታላቅነት ለማፅናት በአንድነት በመቆም ማክበር አለብን ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
በዓላቱ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆኑ ከንቲባው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!