Fana: At a Speed of Life!

የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ባለሐብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ባለሐብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ ቀረበላቸው፡፡

የኢፌዴሪ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ÷ ከተባበሩት ዓረብ ኤሜሬቶች ባለሐብቶች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን ገለጸዋል፡፡

በውይይታቸውም ÷አዋጪ እና ክፍት በሆኑ የንግድ አማራጮች ላይ ገለጻ ማድረጋቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም ÷ኮሚሽነሯ መንግስት በዘርፉ ላይ ያደረገውን ማሻሻያዎች እና ማበረታቻዎች ለባለሃብቶቹ ማስረዳታቸው ተጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.