Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ ከደቡብ ሱዳን የፖሊስ አገልግሎት ኃላፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ የፖሊስ አገልግሎት ኃላፊ ኢንስፔክተር ጀነራል ማጃክ አኬችንና ልኡካን ቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል ፡፡

በውይይታቸውም ÷ የተደራጁ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በተቀናጀ የሁለትዮሽ ጥምረት ለመመርመር በሚያስችል መልኩ ለመስራት ስምምነት ላይ መደረሱን ከፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ልዑካን ቡድኑ በወንጀል ምርመራ ቢሮ የተሰሩ የሪፎርም ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን ፥ በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የወንጀል ምርመራን፣ የተጠርጣሪ አያያዝ፣ የዲ ኤን ኤ ላብራቶሪንና የዲጂታል ፎረንሲክ ምርመራን በአካል ተዘዋውረው መጎብኘታቸው ተገልጿል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.