በትግራይ ክልል ከ60 ሺህ በላይ ተማሪዎችን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመፈተን ዝግጅት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ60 ሺህ በላይ ተማሪዎችን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመፈተን ዝግጅት መደረጉን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡
በቢሮው የምዘናና ብሄራዊ ፈተናዎች ዳይሬክተር ክንፈ ፍስሃ ለኢዜአ እንደገለፁት ÷ ለዘንድሮ የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተማሪዎችን ዝግጁ የማድረግ ስራ ተከናውኗል፡፡
ፈተናው በክልሉ በ75 ወረዳዎች ከሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ .ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥም ነው ያረጋገጡት፡፡
ለፈተናው የሚቀመጡ ተማሪዎች በ2012 ዓ. ም የመጀመሪያ መንፈቅ ትምህርት የተከታተሉና ዘንድሮ በተጀመረው ትምህርት የቀጠሉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡
ተማሪዎቹ ከመደበኛ ክፍለ ጊዜ በተጨማሪ በእረፍት ጊዜያቸው ሁሉ የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጣቸው መቆየቱን አብራርተዋል፡፡