Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ የክረምት ትራፊክ በጎፍቃድ አገልግሎት የሚያስተባብሩ 5 ሺህ በጎፍቃደኞች የስራ ስምሪት ወሰዱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የክረምት ትራፊክ በጎፍቃድ አገልግሎት የሚያስተባብሩ 5 ሺህ በጎፍቃደኞች ዛሬ የስራ ስምሪት ወሰዱ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ስምሪቱን ሰጥቷል፡፡

5 ሺህ በጎፍቃደኞች በክረምት የትራፊክ በጎ ፍቃድ ተግባሩን እንደሚያስተባብሩም የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

በስምሪት አሰጣጥ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተሳተፉ በጎፍቃደኞች የደም ልገሳ ፕሮግራም ማካሄዳቸውም ተገልጿል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.