Fana: At a Speed of Life!

በአዳማ ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ከ3 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ 111 ፕሮጀክቶች ተመረቁ፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የአሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አወሉ አብዲ እና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ዛሬ ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል÷ የኦሮሚያ ልማት ማኅበር (ኦልማ) ሕንጻ፣ የአዳማ ከተማ ዘመናዊ መናኸሪያ እና የኢፈ ቦሩ ትምህርት ቤት ይገኙበታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.