Fana: At a Speed of Life!

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት 500 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር ተከላ መርሐ ግብር እየተሳተፉ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች 500 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር ተከላመርሐ ግብር በየካ ክፍለ ከተማ ፈረንሳይ 01 አካባቢ እያከናወኑ ነው፡፡

የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ ÷ በኢትዮጵያ የተጀመረው የአረንጓዴ ልማት ዘመቻ ለአፍሪካ ብቻ ሣይሆን ለዓለም ተምሳሌት የሚሆን ነው ብለዋል፡፡

የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ÷ የአረንጓዴ ልማትን እውን በማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአየር ብክለት ጋር ተያይዞ የሚከሰተውን ቀውስ ለመቀነስ ዘመቻው አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.