Fana: At a Speed of Life!

ሲ ሲ ኢ ሲ ሲ የተሰኘው የቻይና ኩባንያ በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢንቨስት ለማድረግ ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡና ማቀነባበር ላይ የሚሰማራ ሲ ሲ ኢ ሲ ሲ የተሰኘ የቻይና ኩባንያ በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያስቸለውን ስምምነት ዛሬ ፈርሟል፡፡

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ተሬሳና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈፃሚ ሽፈራው ሰለሞን ከሲ ሲ ሲ ኢ ሲ ሲ ኩባንያ ተወካዮች ጋር ስምምነቱን ፈርመዋል፡፡

ኩባንያው በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢንቨስት በማድረግ በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን የቡና ምርት ማቀነባበር ላይ ይሰራል መባሉን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.