Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ማህበረሰቡ የዓይን ብሌኑን በመለገስ ለወገኖቹ ብርሃን እንዲሆን ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ዜጎች ከህልፈት በኋላ የዓይን ብሌናቸውን በመለገስ ለሌሎች ወገኖቹ ብርሃን እንዲሆን ጥሪ አቀረቡ፡፡

ፕሬዚዳንቷ የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ የተመሰረተበት 20ኛ ዓመት አከባበር ላይ እንደገለጹት÷ ማህበረሰቡ ስለ ዓይን ልገሳ ያለውን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ ማከናወን ይገባል፡፡

ከህልፈት በኃላ በሚደረገው ልገሳ ምንም የምናጣው ነገር አይኖርም ያሉት ፕሬዘዳንቷ÷ ብርሃንን የመሰለ ታላቅ ስጦታ ትኩረት ሊነፈገው አይገባም ብለዋል፡፡

ስለሆነም ዜጎች ከህልፈት በኋላ የዓይን ብሌናቸውን በመለገስ ለሌሎች ወገኖቻቸው ብርሃን እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው÷ የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ የበርካታ ሰዎችን ህይወት የለወጠ ተቋም ነው ሲሉ አውስተዋል፡፡

እስካሁን የዓይን ባንኩ ባደረገው እንቅስቃሴ ከ3 ሺህ ለሚበልጡ ወገኖች ብርሃናቸውን መመለስ መቻሉን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.