የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለጸጥታ አመራሮች ሹመት ሰጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ ጸጥታ አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መሰረትም ፡-
1. ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ወልዴ – የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
2. ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ ገ/መስቀል- የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
3. ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ ገዳሙ- የአብክመ ማረሚያ ቤቶች አገ/ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ዶ.ር እሸቱ የሱፍ አየለ – በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
5. ደጀኔ ልመንህ በዛብህ – በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
6. በሪሁን መንግሥቱ ከበደ – የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
7. ዳኛው በለጠ ጎኔ – የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
8. ገደቤ ኃይሉ በላይ – የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
9. ኮሚሽነር ውበቱ አለነ – የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኃላፊ
10. ኮማንደር አያልነህ ተስፋዬ – የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሰው ኃይል አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ
11. ም/ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ – የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሎጀስቲክስ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡