የሰንደቅ ዓላማ ቀን በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተከበረ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 16ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በተለያዩ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተከብሯል፡፡
ቀኑ “የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተከበረው፡፡
በኦሮሚያ ክልል በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶች የመንግስት ስራ ሃላፊዎች እና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል፡፡
የጨፌ ኦሮሚያ አፈጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ክብርና መገለጫ መሆኑን አንስተው፥ ቀደምት አባቶች ኢትዮጵያን ለማፅናት ለሰንደቅ ዓላማ ክብር ሲሉ ትልቅ መስዋዕትነት መክፈላቸውን አስታውሰዋል።
በተመሳሳይ በሲዳማ ክልል፣ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 16ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በተለያዩ ሁነቶች የመንግስት ሰራተኞ እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ተከብሯል፡፡
በወንድሙ አዱኛ እና ጥላሁን ይልማ
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
በመወዳጀት ይከታተሉን፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!