በትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ዳሌ ሰዲ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የስምንት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
የወረዳው ትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት የትራፊክ ደኅንነት ተቆጣጣሪ አረጋ መንገሻ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ዛሬ ጠዋት 2፡00 ገደማ በደረሰው የትራፊክ አደጋ በአራት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
አደጋው የተከሰተው÷ በተለምዶ ‘ዶልፊን’ እየተባለ የሚጠራው መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ‘ኤፍ ኤስ አር’ ተብሎ ከሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ነው ብለዋል፡፡
በገላና ተስፋ
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!