Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ116ኛው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ያስተላለፉት መልዕክት ዋና ዋና ነጥቦች

-እንደስሙ የመከላከያ ሠራዊት የሆነው ኃይላችን በመቶ አመት ታሪኩ ማጥቃትን፣ መግደልን፣ ማጥፋትን ታሳቢ አድርጎ ሰርቶ አያውቅም፤
-መከላከያ ሠራዊት በራሱ ተነሳሽነት ማንንም አጥቅቶ አያውቅም አሁንም ማንንም አያጠቃም፤
-የሀገር መከላከያ ሠራዊት በሀገር ውስጥ እና በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በኮሪያም እንዳሳየው የሰላም አስከባሪ ሆኖ ላለፉት በርካታ ዓመታት ሰርቷል፤ አሁንም የሰላም አስከባሪ ሆኖ በሀገር ውስጥና በውጭ ይሰራል፤
-ሰላም ከማስከበር፣ ሰላም ከማፅናት፣ ሰላም ከመጠበቅ፣ የሀገር ብልፅግና እንዲቀጥል ከማድረግ ውጭ የሀገር መከላከያ ሌላ ተልዕኮ የለውም፤
– ኢትዮጵያ በኃይልና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም፤
-ለጋራ ጥቅም፣ ለጋራ እድገት፣ ለጋራ ብልፅግና ሁሉንም አሸናፊ በሚያደርጉ ጉዳዮች ከወንድሞቻችን ጋር ተወያይተን የጋራ ጥቅም የምናስከብር እንጂ በኃይል ፍላጎቶቻችንን ለማሳካት ወንድሞቻችን ላይ ቃታ የምንስብ አይደለንም፤
-ኢትዮጵያን ማፍረስ፣ የኢትዮጵያን ተቋም ማፍረስ፣ የኢትዮጵያን አብሮነትንና ወንድማማችነትን ማፍረስ፣
ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ቢሆን ያልተገባ ተግባር በመሆኑ ትምህርት ልንወስድበት ይገባል፤
-ኢትዮጵያ ታሪክ ጠገብ ትልቅ ሀገር ናት፤ መከላከያ ሠራዊት ብቻ እንኳን 116 ዓመት የሚለውን ስንት ሀገር በዚህ ደረጃ ሊጠራ እንደሚችል እርግጠኛ አይደለሁም፤
-ይህንን የተከበረ ሀገር እና ተቋም ማፅናትና መጠበቅ ልዩነት ካለም በውይይት በድርድር መፍታት መለመድ ይኖርበታል፤
-ወንድም ወንድሙን እየገደለ መቀጠል የለበትም፤
-እኛ መዋጋት እናውቃለን፣ ማሸነፍ እናውቃለን እድሜያችንን በሙሉ ያሳለፍነው በዚህ ነው ነገር ግን በውጊያ ከማሸነፍ በእጅጉ የላቀው በሰላም ማሸነፍ ነው፤
-ከሰራን ሊቀየር የሚችል ሀገር እንዳለን ባለፉት ጥቂት ዓመታት መገንዘብ ችለናል፤
-ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአምስት ዓመት ውስጥ በጦርነት፣ በኮሮና ጫና ሳትንበረከክ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገቷን እጥፍ ማድረግ ችላለች፤
-አላደጋችሁም ለምትሉን የዕድገት መለኪያዎች ላልገባችሁ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በ5 ዓመት ውስጥ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገቷን ደግማለች፤
-ትግላችን ይቀጥላል ማንኛውም ፈተና ከዕድገታችን፣ ከብልፅግና፣ ኢትዮጵያን ከማፅናት ሊያቆመን አይችልም፤
-እያንዳንዱን ፈተና እንማርበታለን፣ እያንዳንዱን ፈተና እንሰራበታለን፣ እያንዳንዱን ፈተና ኢትዮጵያን እናጸናበታለን፣ እያንዳንዱን ፈተና ኢትዮጵያን እንሰራበታለን፤

በታምራት ቢሻው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.