ቻይና በራስ አቅም የሠራቻትን ግዙፍ መርከብ አስተዋወቀች
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የሠራቻት “አዶራ ማጂክ ሲቲ” የተሰኘች ግዙፍ መርከብ ለቀዘፋ መዘጋጀቷ ተሰምቷል፡፡
በዛሬው ዕለት በሻንግሃይ ለዕይታ የቀረበችው “አዶራ ማጂክ ሲቲ አንድ መለስተኛ መንደር” እንደማለት ነች ሲል ቻይና ዴይሊ ዘግቧል፡፡
323 ነጥብ 6 ሜትር ርዝመት ያላት መርከቧ÷ 135 ሺህ 500 ቶን የመጫን አቅም እንዳላት ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም በአንድ ጊዜ 5 ሺህ 246 መንገደኞችን መጫን እንደምትችልም ነው የተመለከተው፡፡
“አዶራ ማጂክ ሲቲ” 2 ሺህ 125 የማረፊያ ክፍሎች እንዳሏት ዘገባው ጠቅሷል፡፡
ግዙፏ መርከብ የመጀመሪያ የንግድ ጉዞዋን በፈረንጆቹ ጥር 1 ቀን 2024 እንደምትጀምር ተነግሯል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!