የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) ለ37ተኛው የአፍሪካ ኀብረት መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል።
ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡