Fana: At a Speed of Life!

የብራዚል ቀዳማዊት እመቤት ጃንጃ ሉላ ዳ ሲልቫ የምገባ ማዕከላትን ጎበኙ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብራዚል ቀዳማዊት እመቤት ጃንጃ ሉላ ዳ ሲልቫ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር በመሆን የተስፋ ብርሃን እና የመቅደላ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የምገባ ማዕከላትን ጎብኝተዋል፡፡

እንዲሁም በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ የተገነባዉን የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናት ማሳደጊያ ማዕከልን ጎብኝተዋል::

 

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ “በቀጣይም የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ይበልጥ አጠናክረን በትብብር አብረን ለመስራት የሚያስችለንን ውይይትም አድርገናል” ብለዋል::

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.