Fana: At a Speed of Life!

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ጋር በትብብር ለመሥራት ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በምርምርና ፈጠራ ሥራ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ስምምነትቱን የፈረሙት የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እና የፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤልያስ ይርዳው ናቸው።

ሳሙኤል (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት÷ ዩኒቨርሲቲው የአምስት ዓመቱን ስትራቴጂ ለማሳካት ከያዛቸው ግቦች መካከል ሀገራዊ ፋይዳ ካላቸው የግል ዘርፎች ጋር በትብብር መሥራት አንዱ ነው።

ከፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ጋር የተደረገው ስምምነትም የስትራቴጂው አካል መሆኑን ጠቅሰው÷ በጥናትና ምርምር እንዲሁም ፈጠራ ላይ በትብብር ይሠራል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የተማሪዎችን የፈጠራ ሐሳብ ወደ ሀብት ለመለወጥ በሚደረገው ጥረትም የስምምነቱ ፋይዳ የጎላ ነው ብለዋል፡፡

ኤሊያስ ይርዳው በበኩላቸው÷ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ስምምነቱ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል።

ግሩፑ ቴክኖሎጂ ነክ የሆኑ በርካታ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ እየሠራ መሆኑን በመግለጽ ስምምነቱ የፕሮጀክቶችን ውጤታማነት ይበልጥ እንደሚያሳድገው አመላክተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.