Fana: At a Speed of Life!

በወዳጅነት ጨዋታ መቻል በኪታራ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመቻልን 80ኛ ዓመት ምሥረታ አስመልክቶ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደውን ጨዋታ የዑጋንዳው ኪታራ ቡድን መቻልን 2 ለ 0 ረትቷል፡፡

የመቻል ስፖርት ክለብ 80ኛ ዓመት ምስረታን አስመልክቶ ቀደም ብለው በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች÷ የአርቲስቶች ቡድን የመቻል የቀድሞ ተጫዋቾችን 3 ለ 0 እንዲሁም የባለስልጣናት ቡድን ባለሃብቶችን 2 ለ 1 አሸንፈዋል፡፡

ፖርቹጋላዊው ሉዊስ ናኒ እና ናይጄሪያዊው ኑዋንኮ ካኑም በስታዲየም ተገኝተው ጨዋታውን ተከታትለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.