ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ለርዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሚ የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላለፉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) የርዋንዳ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን ለ4ኛ ጊዜ ላሸነፉት ፖል ካጋሚ የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ፕሬዚዳንት ካጋሚ ቀጣዩ የሥራ ጊዜያቸው ውጤታማ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡
በቀጣዩ የአመራር ጊዜያቸው ለርዋንዳ የላቀ መረጋጋት እና ልማት እንዲያመጡም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡