Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የ86 ነጥብ 18 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና የህዝብ ፈንድ (ዩኤንኤፍፒኤ) ጋር የ86 ነጥብ 18 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራርማለች፡፡

የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው ከዩኒሴፍ ም/ተወካይ ሪኮ ካጎሺማ እና ከዩኤንኤፍ ፒ ኤ ም.ተወካይ ታይዎ ኦሉዮሚ ጋር ተፈራርመዋል፡፡

ድጋፍ በ2017 የበጀት ዓመት በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሚደረጉ ሀገር አቀፍ መርሐ ግብሮችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚውል ተገልጿል፡፡

ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ 70 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላሩ ከዩኒሴፍ የተገኘ ሲሆን÷የተመጣጠነ ምግብ፣ ትምህርት፣ ጤና፣ የህጻናት ጥበቃ እና የሥርዓተ-ጾታ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚውል ተጠቁሟል፡፡

16 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላሩ ደግሞ ከዩኤንኤፍፒኤ የተገኘ ሲሆነ÷ለቤተሰብ ምጣኔ፣ ለእናቶች ጤና፣ ለወጣቶች ልማትና የሥርዓተ-ኦጾታ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም እንደሚውል መጠቀሱን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.