Fana: At a Speed of Life!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውጤታማ ስራዎችና ተሞክሮዎች ተመዝግበዋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአዲስ መልክ ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ ውጤታማ ስራዎችና ተሞክሮዎች መመዝገባቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ፡፡

የክልሉ የ2016 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በዚሁ ወቅት አቶ እንዳሻው ጣሰው÷ ክልሉ በአዲስ መልክ ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት 11 ወራት በሁሉም ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችና ተሞክሮዎች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡

ስራዎችን በየጊዜው በመገምገምና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡

መድረኩ የተገኙ የልማት ተሞክሮችን በማስፋትና ጉድለቶችን በማረም በተያዘው በጀት አመት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነም ተናግረዋል።

መድረኩ የበጀት አመቱን ስራዎች አፈጻጸም በመገምገም የ2017 በጀት አመት የትኩረት አቅጣጫዎችና ክልላዊ ግቦች ያስቀምጣል መባሉንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.