Fana: At a Speed of Life!

ለ2017/18 የምርት ዘመን የማዳበሪያ ግዥ ሂደት መጀመሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ2017/18 የምርት ዘመን 25 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ መታቀዱን እና የግዥ ሂደቱም መጀመሩን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት የባለድርሻ አካላት የእውቅናና ምስጋና መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው።

በ2016/17 የምርት ዘመን ከ18 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሎች መሰራጨቱን እና ከ87 በመቶ በላይ ለአርሶአደሩ መድረሱን ሚኒስትሩ በመርሐ-ግብሩ ላይ ተናግረዋል፡፡

ወደ ሥራ የገባው አዲሱ የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መመሪያም በተያዘው የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ግዥና አቅርቦት ላይ የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር አስችሏል ብለዋል።

በዙፋን ካሳሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.