ሀድያ ሆሳዕና ንግድ ባንክን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ15ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ እዮብ አለማየሁ የሀድያ ሆሳዕናን ብቸኛ እና የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡን ወደ 26 ከፍ በማድረግ ፕሪሚየርሊጉን መምራት ሲጀምር በሊጉ ደካማ አቋም እያሳየ የሚገኘው ንግድ ባንክ በነበረበት 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
የ15ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብሮች መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ባህርዳር ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡