Fana: At a Speed of Life!

ቻይና በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋን ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በኢትዮጵያ ከቻይና አምባሳደር ቼን ሀይ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በብሪክስ የትብብር ማዕቀፍ መሠረት የሁለቱን ሀገራት ትብብር ለማጠናከርና በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ጥቅም ለማስጠበቅ በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡

አምባሳደር ቼን ሀይ÷ ሀገራቸው የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም እንደምትደግፍና የኢንቨስትመንት ተሳትፎዋንም ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነች ማረጋገጣቸውን ከቻይና ኢምባሲ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.