ስሑል ሽረ እና ወላይታ ድቻ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መርሐ ግብር ስሑል ሽረ እና ወላይታ ድቻ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሠዓት በተካሄደው ጨዋታ ፀጋዬ ብርሃኑ ለወላይታ ድቻ እንዲሁም ብርሃኑ አዳሙ ለስሑል ሽረ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል አመሻሽ 12 ሠዓት ላይ አዳማ ከተማ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር ይጫወታል።